|
|
|
ቅኔ.1 እኛን ሲሉ መጥተው አትጨክኑባቸው ማርካችሁ ገፋችሁ ባዶ አታስቀሯቸው ነጋድራሰ ተሰማ እሸቴ
|
|
ቅኔ.2 እነኝህ ፋሽሽቶች በውነት የዋህ ናቸው የአክሱምን ሀውልት ሮም መውሰዳቸው የመርዙ ምልክት እንዳይሆንባቸው ነጋድራሰ ተሰማ እሸቴ
|
|
ቅኔ.3
የኔታ አካለወርቅ ትምህርት ሚኒስቴር አልማዝ ወርቅ የሚገኝ መሆኑን ከምድር መጽሀፍ ዘርግቶ እንደማስተማር እኔን ተከትሎ ይላል ብር ብር ነጋድራሰ ተሰማ እሸቴ |
|
ቅኔ.4
ባዲሱ መሳሪያ በመስኮቦች እቃ ትስቅብናለች ጎኗን ተጠብስቃ ነጋድራሰ ተሰማ እሸቴ
|
|
ቅኔ.5
ጨክኖ ለመግደል ሆዴ አልችል አለ እንጂ አላማማ ምነው የነፍጠኛ ልጅ ነጋድራስ /ተ/እ
|
|
ቅኔ.6
አለም ሲደላደል ሲከፋፈል በእጣ የኢትዮጵያ አርበኛ ኤርትራን አወጣ ነጋድራስ /ተ/እ
|
|
ቅኔ.7
ሀበሾች አያውቁኝ ምን አስወቀሰኝ አሜሪካ እያለ ሰርቶ እሚያፈርስኝ ነጋድራስ /ተ/እ
|
|
ቅኔ.8
አዳራሹ ሰፊ በሩ አልጠበባችሁ በተራ በተራ ምነው መግባታችሁ ነጋድራስ /ተ/እ
|
|
ቅኔ.9
አሻግራቸውና ከብቶቻችን ይብሉ ያ ሳር አይደለም ወይ የምናየው ሁሉ ነጋድራስ /ተ/እ
|
|
ቅኔ.10
ያራዳ ሴት ሁሉ ዘመድም የለሽ ለፈታሽ ነገርኩት እኔ ላገባሸ ነጋድራስ /ተ/እ
|
|
ቅኔ.11
ሞጣ ቀራኒዮ ምነው አይታረስ በሬ ሳላይ መጣሁ ከዚህ እዚያ ድረስ
|
|
ቅኔ.12
እውቀቱ ሳያንሰው ሳይቸገር ሃብት ፍቅር ተጠናውቶት ከድሃ ባልቴት ታዬ ተኮራምቶ ጠባብ ክፍል ቤት በ ሳ/አ |
|
ቅኔ.13
ምነው እዚያ ማዶ ጭር አለ ሰፈሩ ምነው እንዲህ ውዲህ ስዎች አይጣሩ ለካ ቋንቋ አጥሮት ነው አገሩ መንደሩ በሳ/አ |
|
ቅኔ.14
ባሌ መለሎ ነው ብዬ ሲያቀብጠኝ ድንገት መንገድ ታዬ ጉድ አደረገኝ መዋረዴ አልቀረ አላመለጥኩኝ መለስተኛ ነው ወይ ብለው ጠየቁኝ በሳ/አ |
|
ቅኔ.15
አልጫን ብትለው ዱር ለምዳ አህያው ሁሉን እይው ብሎ ልጓሟን ፈታው ያዳኙን ጭካኔ ተንኮሉን አይታው መሆኑን አመነች አማራጭዋ ሰው በሳ/አ |
|
ቅኔ.16
አህያ ይሉታል የናቁትን ሰው የደደብ ተምሳሌት እኔን አድርገው በጀርባዬ አይደል ወይ አገር ያቀናሁት ምነው ስሜን እንዲህ ለውርደት ዳረጉት በሳ/አ |
|
ቅኔ.17
ማእበል አናውጦት ሸቀጡን ቢያጥበው ቀይ ባህር ነጋዴው ክስረት ገጠመው ዘንድሮ ምን ሆነ ምን ጉድ አገኘው ዋናተኛ ሆኖ ሲያተርፍ ስናቀው በሳ/አ |
|
ቅኔ.18
ለሙግት ለፍልሚያ ቀን ሳይቆርጡለት ድንገት ከጎን ደርሰው ነጠቁት እርስት በሳ/አ
|
|
ቅኔ.19
ልሞ የተፈጨ የደቀቀቅ ጤፍ ነው ተገረዳደፈ የሚለኝ ሰው ማነው (ደራሲው የማይታወቅ)
|
|
ቅኔ.20
ለኔ የሚታየኝ ስላልታያችሁ እረ እናተ ሆዬ ሳቅ ሞትኩላችሁ ነጋድ/ ተሰማ እሸቴ
|
|
ቅኔ.21
አዲስ ጸጋንና ታምራትን ትቶ ያመነዝር ጀመር ዳዊቱን አንግቶ በሳ.አ
|