ካልጠፋ ምራቅዎ!!
|
በጠ/ሚ ገምጋሚነት የተወካዮች ምክር ቤት አባላት እየተገመገሙ ሣለ ጠ/ሚ ድንገት ሲጋራ ያልቅባቸውና የአማራውን ክልል ፕሬዘዳንት 10 ብር ሰጥተው ይህቺ ምራቅ ሳትደርቅ ሲጋራ ገዝተህ ና ብለው ይልኩታል; የአማራው ፕሬዘዳትም ምራቋ ሳትደርቅ ለመድረስ እንደ ንፋስ ብንንንንንንንንን እያለ ልቡ 999 እየመታ ሮጦ ገዝቶ ሲመለስ እንዳሰበው ሳይሆን ምራቋ ደርቃ ይደርሳል;;
ጠ/ሚም ቆጣ ብለው...<<
ምን ነበር
ያልኩት? ምራቋ ሳትደርቅ
ብዬ አልነበርም >>
ብለው ያፈጣሉ? ጠ/ሚርም <<< ይህን ብቻዬን መወሰን አልችልም ለምክር ቤቱ አቅረበዋለሁ >> በማለት ጉዳዩን ለፓርላማ ያቀርባሉ; የኢሃዴግ አባሎች ሁሉ አዲሱ ለገሰን እየወቀሱ አስተያየት ከሰጡ በኋላ አንድ የተቃዋሚ ድርጅት መሪ እጃቸውን ያወጡና አስተያየት አለኝ ይላሉ; ጠ/ሚርም እድል ይሰጣሉ ; የተቃዋሚው ድርጅት መሪም ቀጠል አድርገው << አዲሡ ለገሰ አሁን ምን ኣጠፋ ብለው ነው ? የሮጠበት የልቡ ትርታ ከረባቱን እስኪያርገበግበው ድረስ እየታየ አሁን እሱን መቅጣት ተገቢ ነው? ጥፋቱ ያለው እርስዎ ጋ ! ከሞላ ምራቅዎ ምስር የምታክል ተፍተው እንጂ በአፍታ መድረቋ እሱማ ምን አደረገ በማለት ጠ/ሚርን በአሽሙር አጠናፈሯቸው; ቁጭ.../..... |
