|
ያቺ የአንድዬ ምሩቋ - ቀለም ያልገባት እናቴ
አጥና ልጄ ትለኝ ነበር - ፊደል አቅርባ ከፊቴ
ለየኔታ ትከፍለው ዘንድ -አንድ ሽልንግም ቸግሯት
ከእውቀት ገበያ ቀርቼ -ልጅዋ ከቤት ብውልባት
ልቧ በቁጪት በልዞ - የምታደርገው ቢጠፋት
ያቺ የአንድዬ ምሩቋ -ቀለም ያልገባት እናቴ
ሀ
በል ልጄ ትለኝ ጀመር -ፊደል አቅርባ ከፊቴ
በቃል ፊደል ቆጠራዋም ከ
ሀ እስከ
ሆ
እየደገመች
በጠቋሚው ስንደዶዋ ከ
በ እስከ
ቦ
እየተመመች
ሀ
በል ልጄ ትለኝ ጀመር - በሳሩ
በ '
እያሳይች
ፊደል አለመለየቷን - ጪንቀቷን መች ተረድቼ
ሆ
ማለቴን ቀጠልኩ እንጂ - ጣቴን በ
ቦ "ላይ
ሰክቼ
በአሻሮ ጪስ ተጨናብሳ - ምስኪኗ እምዬ የኔ እናት
ያቺ መከረኛ ሽልንግ - ከመዳፍዋ ስትገባላት
ወደ የኔታ ስትወስደኝ - መቼ በወጉስ ነጋላት
ከአናት
ሀ
ን እየጠቆሙ
ሀ በል ሲሉኝ የኔታ
እኔም ከእናቴ ባወቅኩት
በ ን እየጠቆምኩ ሳምታታ
በቁንጥጫ መዠለጉኝ - ጭኔ ከእንጆሪ እስኪቀላ
ሚጢጢዋ ልቤ አዝና -መፈጠርዋን እስክትጠላ
ፊደል አለመለየቷን - ችግሯን መች አውቄላት
አስቆነጠጥሽኝ ብዬ እንጂ - የቁም ስቅሏን
ያሳየኋት
ታዲያ ለዚህች ለናቴ ፊደል ላልዘለቀች ምስኪን
ምን መንፈስ ይሆን ሹክ ያላት እውቀት ብሩህ ተስፋነቱን ?
ያቺ ያንድዬ ምሩቋ -ቀለም ያልገባት እናቴ
አጥና ልጄ ትለኝ ነበር - ፊደል አቅርባ ከፊቴ
ሳ/አ
|