Poems                                                 ግጥም

  Back Home      Articles          Poems           News              Jokes               Email Us

        THIS WEBSITE IS CURRENTLY BLOCKED IN ETHIOPIA

              ይድረስ ለገነት ዘውዴ ትምህርት ምኒስትሯ

               ከእንግዲህ ትውልድ ሁሉ እርኩሲት ይሉሻል

                                       
                                              
                                 

ወይዘሮ ልበልሽ ክቡርት

አንቱ ልበል አንቺ ገነት

ለሴትማ ለወላድ ወይዘሮ አይደል ወጉ ?

የአጠራር የስም ማረጉ

ግን እንቢ አለኝ ቃሉ

ወይዘሮን ላንቺ መቀጠሉ

ከአለት ጠጥሮ አንጀትሽ

እንዴት ወይዘሮ ልበልሽ ?

የአዛኝ የወላድ ስም ልስጥሽ

ባንቺ ጥሪ! ባንቺ ምሪት! ባንቺ እንቢታ!

በእበላባይ ሎሌነትሽ ለስልጣን ጥማትሽ ርካታ

የጨቅላ ደም እንደ ውሃ ከጎዳና ቦይ ተቀዳ!

ገላው በጥይት ዳታርፎሖቦ ዳግም ለግዞት ተነዳ

አንቺም ለተቀመጥሽበት ወንበር

ለስልጣንሽ እዳ ግብር

የጨቅላ ደም ጭዳ ሰጥተሽ

ዛሬም ክብርት ትባያለሽ

አዬ ክብርት..! አዬ ክብር ...!

አይ ወይዘሮ አዬ ምሁር

ደም ባቀረዘዘው ብእርሽ

ትውልድ በማይረሳው ፊርማሽ

በስመ ኢሃድግ ወ ወያኔ ባርከሽ

የወጣቱን እርድ ፈቀድሽ

ዳግም ስትኮፈሽበት አልከረፋሽም ወንበርሽ

በለጋ ደም የጨቀየው ትንሽም አልሰነፈጠሽ

ዳሩ እለት በእለት ለሚያርድ ሰው

የትኩስ ደም መአዛ እንጂ

ክርፋቱ እንዴት ሊሰማው ?

መሃጸን ፍሬ መስጠቱ የሴት ወጓናውና

አንቺም መቼም በተፈጥሮ ሴት ነሽና

ፍሬ አፍርተሽ የወላድ ወጉ ከደረሰሽ

እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ

እንደ ደራሽ ውሃ ሲሮጥ የልጅዋ ደም በጎዳና

የተመለከትች እናት እንዴት ነው የምትጽናና ?

ለአንድ አፍታ ወላድ ሆነሽ እስኪ አስቢው

ገላው በጥይት ተቦዳድሶ

ደሙ ባፈር ተለውሶ

አፈር ልሶ

ልጅሽን ጎዳና ብታይው

እንዴት ይሆን ስሜትሽ ?

እኮ ምን ይሆን መልስሽ ?

ዳሩ የወላድ አንጀት ቀድሞውኑ መች ኖሮሽ

አዬ ክብርት አዬ ክብር

በደም በጨቀየ ወንበር

ከእንግድህ ትውልድ ሁሉ እርኩሲት ይሉሻል

ይፋረዱሻል ! ይጠይቁሻል!የሞግቱሻል

ገነት ጉዲት ይልሻል

ጉድ ነሽና ይገባሻል

                                          (በሳ.አ)