News                                                      Archive

Back Home               Articles              Poems           News              Jokes               Email Us

እናትዎስ እንኳን ሞቱ

እናትዎስ እንኳን ሞቱ! …

                                                                

                                                                      በሠለሞን  (ከU.K)

እናትዎስ እንኳን ሞቱ! … ዳግም ፍሬ ሳያፈሩ፣

አንድ ነቀርሳ ተክለዋል… የሚበቃ ለሀገር- ምድሩ፣

ግና!! ...... በኔ ግምት...! በኔ እሳቤና ምልከታ፣

እርስዎን ሊወልዱ ማልነበር..? የተላመኑት ከጌታ!

መልካም ሲሆን እንጂ ፍሬ!! ለወላጅም የሚያኮራ፣

ቀና ሲሆን እንጂ ትሁት - ያባቱን ስም የሚያስጠራ

መች የትቢት! መሰሪ ሊቅ?  ጭንጋፍ የተንኮል ደብተራ!

 ለፍሬ ባይለው ባያድለው! የናትዋ ተማጽኗቸው፡

በፍጡር ደም የሚታጠብ የግፍ -አጋፋሪ ሰጣቸው!!

አዎ!!!!!......................

እናትዎስ እንኳን ሞቱ! … ዳግም ፍሬ ሳያፈሩ፣

አንድ ነቀርሳ ተክለዋል… የሚበቃ ለሀገር- ምድሩ፣

 

እንኳን ሞቱ!! እንኳን ሞቱ… ቆመው ከሚያዝኑ በልጃቸው

ኖረው ከማልቀስ በፍሬአቸው…አፈር ምስጡ ነው ሚሻላቸው

 

ምንነትዎም ከማይለየው...ከርስዎ አይነቱ አካይስት!!

አያ ጅቦ እንኳ ይራራል! ያ ስመ ጥፉ አራዊት ! !
 

አዎ!!!!!

እናትዎስ እንኳን ሞቱ! … ዳግም ፍሬ ሳያፈሩ፣

አንድ ነቀርሳ ተክለዋል… የሚበቃ ለሀገር- ምድሩ፣


                back to main page