ጀግና ውለጅ ባክሽ!

 

                             በአስራደው (ፓሪስ/ፈረንሳይ)

የምሁር መሃይም ተባይ አላዋቂ፤
የመሃይም ኩፍስ አስመሳይ አዋቂ ፤
ያአንበሳ ልክስክስ ልፋጭ የሚያላምጥ ፤
የጅብ ባለግዜ ታፋ መራጭ ከሽንጥ
የቁራ እርግብ መሳይ ሰላምን አብሳሪ ፤
የፈረስ አዝጋሚ የግመል ሰጋሪ.፣
የባዕድ ባለቤት የነባር ባይተዋር፤
ሥልጡን ሥራ ፈቶ ሞያ ቢስ ሲገብር ፤
ልማድ ሆኖ ቀረ አቀርቅሮ መኖር ፤
በተወለድንበት በኢትዮጵያ ምድር ፤
ያቀረቀረ ራስ ቀና እንዲል ካንገቱ ፤
ተመልሶ እንዲከብር የሰው ሰውነቱ ፤
ከወደቅሽበት ማጥ ካዘቅጥ እንዲያወጣሽ
ዛሬም እንደ ትናት እንዲታደስ ክብርሽ
እምዬ ኢትዮጵያ ጀግና ውለጅ ባክሽ!!
እምዬ ኢትዮጵያ ጀግና ውለጅ ባክሽ!!


ወይኔ...


                           በአስራደው (ፓሪስ/ፈረንሳይ)

ወይኔ ወይኔ....!
በዘመነ ወያኔ...!
ምን ይበላል ጓያ..!
ምን ይጨሳል ጋያ..!
ምን ይወለዳል አህያ..!
ምን ይሰማል እብለት..!
ምን ይሠራል ጥፋት..!
ምን ይዘንባል እንባ.!
ምን ይበቅላል ገለባ..!
ወይኔ ወይኔ ......!
በዘመነ ወያኔ ...........!